እለቱ ጥር 27 ቀን 2003 ዓ.ም. ጉዞ ወደ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 07/08 ወደ ወይዘሮ ሮማን አያሌው ቤት ጎራ አልኩ፡፡ ከዚያም የተለመደው የእግዚአብሔር ሰላምታዬን አቀረብኩ፡፡ እሳቸውም ከሚሰሩበት ጓዳ ብቅ በማለት ግቢ እግዚአቢሔር ይመስገን ብለው ለሰላምታዬ ምላሽ ሰጡኝ፡፡ እኔም የመጣሁበትን አላማ በመግለፅ ታሪካቸውን እንዲያወጉኝ ጠየኳቸው፡፡ ከዚያም የሚከተለውን አወጉኝ፡፡
ሮማን አያሌው እባላለሁ ከእናቴ ከወ/ሮ አጥናፏ በለይ እና ከአባቴ ከአቶ አያሌው ገ/ማሪያም በ1937ዓ.ም በአሩሲ ከተማ ልዩ ስሙ ሁሩታ በተባለ ትንሽ መንደር ተወለዱኩ፡፡