• We Strive to Empower Poor Women and Girls

wiseadmin's blog

“ ጠንክረን ከሠራን ነገም ሌላ ቀን ነው”

የተወለድኩት ጎንደር አውራጃ ልዩ ስሙ አርማጭሆ ተክል ድንጋይ ይባላል፡፡ በ1958 ዓ.ም ከእናቴ ወ/ሮ ፀጋነሽ ጀንበሬ እና ከአባቴ አቶ ዳኞቸው ወንዳፍራው ተወለድኩኝ፡፡ የአንድ ዓመት ልጅ እያለሁ እናትና አባቴ በመለያየታቸው ምክንያት አባቴ ሌላ ሚስት አገባ፡፡ እኔም ለጥቂት ጊዜ ከእናቴ ጋር ከኖርኩኝ በኋላ ለአባቴ የነበረኝ ፍቅር ከባድ ስለነበረ ከአባቴና ከእንጀራ እናቴ ጋር መኖር ጀመርኩ፡፡ያ ኑሮ ግን የስቃይ ኑሮ ነበር ፡፡

“በልጅነቴ ባገኘሁት ኖሮ”

እለቱ ጥር 27 ቀን 2003 ዓ.ም. ጉዞ ወደ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 07/08 ወደ ወይዘሮ ሮማን አያሌው ቤት ጎራ አልኩ፡፡ ከዚያም የተለመደው የእግዚአብሔር ሰላምታዬን አቀረብኩ፡፡ እሳቸውም ከሚሰሩበት ጓዳ ብቅ በማለት ግቢ እግዚአቢሔር ይመስገን ብለው ለሰላምታዬ ምላሽ ሰጡኝ፡፡ እኔም የመጣሁበትን አላማ በመግለፅ ታሪካቸውን እንዲያወጉኝ ጠየኳቸው፡፡ ከዚያም የሚከተለውን አወጉኝ፡፡
ሮማን አያሌው እባላለሁ ከእናቴ ከወ/ሮ አጥናፏ በለይ እና ከአባቴ ከአቶ አያሌው ገ/ማሪያም በ1937ዓ.ም በአሩሲ ከተማ ልዩ ስሙ ሁሩታ በተባለ ትንሽ መንደር ተወለዱኩ፡፡

Syndicate content